የውሃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ለከተሞች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እንዲሁም ለሰፋፊና መካከለኛ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውል ፋይናንስ ከፌደራል መንግስት ከውጭ አበዳሪና እርዳታ ሰጪ ተቋማትና አገሮች እያፈላለገ የህብረተሰቡን የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ ከውሃ ዘርፍ አስተዳደር ፖሊሲና ስትራቴጂ መርሆች አንዱ በሆነው ዋጋን በማስመለሰ መርህ (cost recovery principle ) ላይ በመመስረት ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በረጅም ጊዜ እና በአነስተኛ ወለድ የሚከፈል ብድር ለመስጠት ታስቦ በጥር ወር 1994 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 268/1994 የተቋቋመ መንግስታዊ ተቋም ነው ፡፡
የከተሞች የመጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን አገልግሎት ሽፋን ለማሳደግ እና የመስኖ ልማትን ለማስፋፋት እንዲቻል ከተለያዩ የፋይናንስምንጮች የሚገኘውን ገንዘብ የብድር መስፈርት ለሚያሟሉ የከተሞች ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች እና ለመስኖ ውሃ ተጠቃሚ ማህበራት ብድር መስጠት ብሎም ብድሩን በወቅቱ በመሰብሰብ ለሌሎች ተመሳሳይ የልማት ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል የተዘዋዋሪ ፈንድ ክምችት መፍጠር ነው ፡፡
በ2017 ዓ.ም ለከተሞች የመጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን ልማት ግንባር ቀደም የፋይናንስ ተቋም መሆን ነው